የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ሰራተኞች 20ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በፓናል ውይይት አከበሩ
*************************
(ት/ማ/ባ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም) ፣-የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የበላይ አመራሮችና የማእከል ሠራተኞች 20ኛውን የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በዛሬው እለት በዋናው መ/ቤት አዳራሽ በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡
የውይይት መድረኩ የተከፈተው የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙርን በመዘመር ሲሆን በመቀጠልም የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበው ሚደቅሳ እለቱን አስመልክተው ንግግር አድርገዋል፡፡

በየዓመቱ ብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ስናከብር ህዳር 29፤ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የጋራ የቃል ኪዳን እና የህጎች ሁሉ የበላይ በሆነው ህገመንግስት መብታቸው የተረጋገጠበት እለት መሆኑን እያስታወስን ነው ብለዋል፡፡
በመቀጠልም “ዴሞክራሲ እና የፌደራል ስርዓት በኢትዮጵያ፤ ተስፋዎቹ እና ተግዳሮቶች” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ የፓርኪንግ ልማትና አስተዳደር ዳይሬክተር በአቶ ቢኒያም ጌታቸው ቀርቦ የበላይ አመራሮችና ሰራተኞች ተወያይተውበታል፡፡

ኢትዮጵያ የተለያየ የብሔር ማንነት ያላቸው ህዝቦች በጋራ የሚኖሩባት ሀገር በመሆኗ፤ ሀገራዊ አንድነታችንን አስጠብቀን በአብሮነት ለመዝለቅ፣ ሁልጊዜም ብዝሃነትን ማክበርና እኩልነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ በተወያዮች ተጠቁሟል፡፡
በበላይ አመራሮች በአቶ ክበበው ሚደቅሳ እና በአቶ አማረ ታረቀኝ በተሰጠ ማጠቃለያም የመንግስት ሰራተኛውም ፌደራሊዝምና ህብረ ብሄራዊነት በሚየጠናክር እና በሀገራችን ሊያሳድጉ በሚችሉ ልማቶች በመሳተፍ ስኬቶችን ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
እንዲሁም በስራ ቦታ ዝቅ ብሎ በማገልገል ከውይይቱ በኋላም መውሰድ ያለበትን በመውስድ የብሄር ብሄረሰቦች እርካታ የሚያረጋግጥ ተግባር ከእያንዳንዱ ሲቪል ሰርቫንት እንደሚጠበቅ አስገንዝበው የውይይቱ መርሃ ግብር ተጠናቋል፡፡
