591547368_1333411855496490_1854987514821260841_n

Addis Ababa Traffic Management Authority is reviewing its 5th week performance on the 2nd quarter rapid response plan.

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በ2ኛ ሩብ ዓመት ፈጣን ምላሽ አምጪ እቅዱ ላይ የ5ኛ ሳምንት የስራ አፈጻጸሙን በመገምገም ላይ ይገኛል።
(ት/ማ/ባ) ህዳር 20/2018ዓ,ም/ 4:10)
ለበለጠ መረጃ ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ
https://linktr.ee/aatma1
ነፃ የስልክ መስመር
696ን ይጠቀሙ


Addis Ababa Traffic Management Authority is reviewing its 5th week performance on the 2nd quarter rapid response plan.
(T/MA/BA) November 20/2018, 4:10)
For more information, click on the link below
https://linktr.ee/aatma1
Toll-free hotline
Use 696

591740924_1334971692007173_7368978511988533550_n

የባለሥልጣን መ/ቤቱ ሰራተኞች የወርቃማ ሰኞ የማለዳ መርሃ-ግብርን አካሄዱ

የባለሥልጣን መ/ቤቱ ሰራተኞች የወርቃማ ሰኞ የማለዳ መርሃ-ግብርን አካሄዱ
• ስለ ተቋሙ የሰራተኞች የሥራ ሰዓት አከባበር ዙሪያ ላይም ውይይት ተደርጓል
**********************
(ት/ማ/ባ ህዳር 22/2018ዓ.ም)፡-የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን የበላይ የሥራ ኃላፊዎችና የማዕከል ሰራተኞች የእውቀት ሽግግርና የልምድ ልውውጥ የሆነውን የወርቃማ ሰኞ የማለዳ መርሃ-ግብር በተቋሙ መሰብሰብያ አዳራሽ አካሂደዋል፡፡
በእውቀት ሽግግርና የልምድ ልውውጥ መርሃ-ግብሩ ላይ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት አገልግሎት አሰጣጥ ክትትል እና ድጋፍ ዳይሬክተር አቶ ሐጎስ ካህሳይ ስለ ‹‹ቅን መሪ›› ምንነት አስመልክቶ ሰነድ አቅርበዋል፡፡


በሰነዱም ላይም ስለ ቅን መሪ ምንነት፣ ባህሪያትን ከባለሥልጣን መ/ቤቱ ስልጣንና ተግባር እንዲሁም ራእዩ ጋር በማዛመድና ምሳሌዎችን በመጥቀስ ለማዕከሉ ሰራተኛ አብራርተዋል፡፡
መሪነት ከራስ እንደሚጀምርና ቅንነት ያለው መሪ በሰራተኞች መካከል መቻቻል እንዲፈጠር ማድረግ፣ የእያንዳንዱን ስራ ማበረታታት ስራውን ባለማጣጣል፤ ምስጋና በመስጠትና በማነቃቃት ለአንድ አላማ እንደቆሙ ማድረግ እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡
በመቀጠልም በባልስልጣን መ/ቤቱ የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ኢዶሳ የተቋሙ ሰራተኞች የሥራ ሰዓት አከባበርና እየተወሰዱ ባሉት እርማጃዎች ዙሪያ ተቋሙ ያለበትን ሁኔታ ሰነድ አቅርበው ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
በመጨረሻም የባለሥልጣን መ/ቤቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ኤልያስ ዘርጋ ባስተላለፉት መልዕክት ለተቋሙ ራእይ ማሳካት ከታች እስከ ላይ ያለ ሰራተኛ በቅንነትና በታማኝነት በመቀናጀት በአንድ ዓላማ የተቋሙን ራእይ ለማሳካት መጣር ይገባዋል ብለዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ
https://linktr.ee/aatma1
ነፃ የስልክ መስመር
696ን ይጠቀሙ