590064786_1333578992146443_1624276497491643228_n

በባለስልጣን መ/ቤቱ በ2ኛው ሩብ ዓመት ፈጣን ምላሽ አምጭ እቅድ የ5ኛ ሳምንት የስራ አፈጻጸም ተገመገመ

(ት/ማ/ባ ህዳር 20/2018 ዓ.ም):_
በአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በተያዘው በጀት ዓመት 2ኛ ሩብ ዓመት በፈጣን ምላሽ አምጭ እቅድ መሰረት የ5ኛ ሳምንት የስራ አጻጸም ሪፖርት ላይ የበላይ አመራሮች፣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጆች፣ የማእከል የስራ ሃላፊዎችና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት የቁጥጥርና የፖርኪንግ ዳይሬክተሮች በተገኙበት ተገምግሟል።
ተቋሙ በ2ኛዉ ሩብ አመት በልዩ ሁኔታ ውጤት ለማስመዝገብ በእቅድ የያዛቸውን የአብይና ንዑስ ተግባራት አፈጻጸም፣ በቁጥጥር እና በፓርኪንግ አስተዳደር ያሉትን ስራዎች፣ የቅሬታና አቤቱታ አፈታት ስርዓት፣ አገልግሎት አሰጣጥና ምቹ የስራ አካባቢን መፍጠር፣ እንዲሁም የገቢ አሰባሰብ እና የመስክ እይታ ሪፖርትን በፎቶና በቪዲዮ አስደግፈው ያቀረቡት የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፤ አግልግሎት አሰጣጥ ክትትል እና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ብሩክ በለጠ ናቸው።
የተግባራቱ ፈፃሚዎችም በቀረበው ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ በየሳምንቱ የተግባራት መሻሻሎች ቢኖርም በቀጣይ ሳምንታት በሪፖርቱ የተጠቆሙትን አንዳንድ ክፍተቶችን በመሙላት የተሻለ ውጤት እንደሚያስመዘግቡ ጠቁመዋል።

የበላይ አመራሮችም ፈጣን ምላሽ አምጪ እቅድ ወደ ተግባር ሲለውጥ መድበኛ ሰዓትን ብቻ መጠቀም ሳይሆን በተጨማሪ ጊዚያቶችም በመስራት ከሂደት አልፎ ለውጥና ውጤት መታየት አለበት ብለዋል።
በመጨረሻም ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበው ሚደቅሳ በቀሪ ሳምንታት ለውጦችንና ጥንካሬዎችን ይዞ መቀጠል፣ ተጠያቂነትን ማስፈን፣ ክፍተቶችን ማረም፣ ክዋኔ ላይ ማተኮር፣ ተደራራቢ ውጤቶችን ማስመዝገብ፤ ብለው ያስቀመጧቸውን አቅጣጫዎች ተሳታፊዎች በሙሉ ድምፅ በመቀበል መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።
ለበለጠ መረጃ ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://linktr.ee/aatma1
ነፃ የስልክ መስመር
696ን ይጠቀሙ

591575960_1335978048573204_828467503311683801_n

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ሰራተኞች 20ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በፓናል ውይይት አከበሩ

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ሰራተኞች 20ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በፓናል ውይይት አከበሩ
*************************
(ት/ማ/ባ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም) ፣-የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የበላይ አመራሮችና የማእከል ሠራተኞች 20ኛውን የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በዛሬው እለት በዋናው መ/ቤት አዳራሽ በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡
የውይይት መድረኩ የተከፈተው የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙርን በመዘመር ሲሆን በመቀጠልም የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበው ሚደቅሳ እለቱን አስመልክተው ንግግር አድርገዋል፡፡

በየዓመቱ ብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ስናከብር ህዳር 29፤ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የጋራ የቃል ኪዳን እና የህጎች ሁሉ የበላይ በሆነው ህገመንግስት መብታቸው የተረጋገጠበት እለት መሆኑን እያስታወስን ነው ብለዋል፡፡
በመቀጠልም “ዴሞክራሲ እና የፌደራል ስርዓት በኢትዮጵያ፤ ተስፋዎቹ እና ተግዳሮቶች” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ የፓርኪንግ ልማትና አስተዳደር ዳይሬክተር በአቶ ቢኒያም ጌታቸው ቀርቦ የበላይ አመራሮችና ሰራተኞች ተወያይተውበታል፡፡

ኢትዮጵያ የተለያየ የብሔር ማንነት ያላቸው ህዝቦች በጋራ የሚኖሩባት ሀገር በመሆኗ፤ ሀገራዊ አንድነታችንን አስጠብቀን በአብሮነት ለመዝለቅ፣ ሁልጊዜም ብዝሃነትን ማክበርና እኩልነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ በተወያዮች ተጠቁሟል፡፡
በበላይ አመራሮች በአቶ ክበበው ሚደቅሳ እና በአቶ አማረ ታረቀኝ በተሰጠ ማጠቃለያም የመንግስት ሰራተኛውም ፌደራሊዝምና ህብረ ብሄራዊነት በሚየጠናክር እና በሀገራችን ሊያሳድጉ በሚችሉ ልማቶች በመሳተፍ ስኬቶችን ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
እንዲሁም በስራ ቦታ ዝቅ ብሎ በማገልገል ከውይይቱ በኋላም መውሰድ ያለበትን በመውስድ የብሄር ብሄረሰቦች እርካታ የሚያረጋግጥ ተግባር ከእያንዳንዱ ሲቪል ሰርቫንት እንደሚጠበቅ አስገንዝበው የውይይቱ መርሃ ግብር ተጠናቋል፡፡