we graduated from the Food Security and Skills Youth Internship Program

This morning, we graduated from the Food Security and Skills Youth Internship Program, which has transformed 15,492 beneficiaries from dependency to productivity.
Our city, Addis Ababa, is making tangible progress in transforming vulnerable residents from dependency to productivity. This is a testament to the success of our city’s grand vision of “Zero Deprivation and Poverty,” one of the five “Zero Goals” announced by Prime Minister Dr. Abiy Ahmed.


Over the past five years, more than 695,000 residents who were caught up in the Safety Net Program have been transformed into productivity, enabling them to become self-sufficient and support their families.
On the other hand, since the start of work experience in our city in 2014, 49 thousand citizens, including the 8 thousand 852 youth who graduated today, have emerged from poverty and unemployment and have completed their work experience and moved to business ownership and production through the connections created for them.


Dear graduates of today; Our city needs strong young people like you who are diligent, who make the most of the opportunities they have received, who will change their lives for the better, and who will be role models for others. Your hard work so far is a great example of how you will go beyond yourself and create job opportunities for others and become business owners with your vision and experience. Be strong!
May the Creator bless Ethiopia and its people!
Mayor Adanech Abebe

 

ዛሬ ማለዳ በምግብ ዋስትና እና ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም 15 ሺህ 492 ተጠቃሚዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር አስመርቀናል።
ከተማችን አዲስ አበባ ለችግር የተጋለጡ ነዋሪዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች። ይህ ተግባር በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይፋ ከተደረጉት አምስቱ የ“ዜሮ ግቦች” መካከል አንዱና ዋነኛው የሆነው “ተረጂነትን እና ልመናን ዜሮ የማድረግ” ታላቅ ራዕይ በከተማችን ስኬታማ እየሆነ መምጣቱን ማሳያ ነው።
ባለፉት አምስት ዓመታት በሴፍትኔት ፕሮግራም ውስጥ ተይዘው ሲረዱ የነበሩ ከ695 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ወደ ምርታማነት በማሸጋገር ራሳቸውን እንዲችሉና ቤተሰቦቻቸውን እንዲደግፉ ተደርጓል።
በሌላ በኩል በከተማችን የሥራ ልምምድ ከተጀመረበት 2014 ዓ.ም ጀምሮ ዛሬ የተመረቁትን 8 ሺህ 852 ወጣቶች ጨምሮ 49 ሺህ የሚሆኑ ዜጎች ከተረጂነት እና ስራ አጥነት ወጥተው በተፈጠረላቸው ትስስር የሥራ ላይ ልምምድ አጠናቀው ወደ ስራ ባለቤትነት እና አምራችነት ተሸጋግረዋል።
ውድ የዛሬ ተመራቂዎች፤ ከተማችን እንደ እናንተ ዓይነት ትጉ፣ ያገኙትን ዕድል አሟጥጠው በመጠቀም ሕይወታቸውን በዘላቂነት የሚለውጡ እና ለሌላውም አርአያ የሚሆኑ ብርቱ ወጣቶች ያስፈልጓታል። በቀጣይም ከራሳችሁ አልፋችሁ ለሌሎች የሥራ ዕድል የምትፈጥሩ እና በሰነቃችሁት ራዕይ፣ ባካበታችሁት ልምድ የድርጅት ባለቤቶች ጭምር እንደምትሆኑ የእስካሁኑ ትጋታችሁ ትልቅ ማሳያ ነው፣ በርቱ !
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
[yarpp]

Leave a comment



Copyright 2025 TMA © All Rights Reserved
Email Address: aartma2011@gmail.com
Phone Number: 696 TMA Free Line  AND  0116672386

Developed by Tewodros Kemal  (@.tk)